ሥጋ ከአብ ፈጽሞ ካነሰ እንደምን በቀኙ ተቀመጠ፤ ሥጋስ ከአብ በእውነት የሚያንስ ቢሆን ገብርኤል በፊቱ በእውነት እንደሚቆም አብ ፊት በቆመ ነበር።
እሱም ሲያስረዳ ከእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ ብሏል። በክብር ያረገው በአብ ቀኝ የተቀመጠው በእውነት ሥጋ ነው። መለኮትስ ምንጊዜም ከዙፋኑ አልተራቆተም።
ሥጋ በአብ ቀኝ መቀመጡ እሱ ከመለኮት ጋር ትክክል ነው። ከፍጡራን በአብ ቀኝ የተቀመጠ ስለሌለ።