አታትዬ ጋሼ ከሞተብን በኋላ በቀስታ አረቄ ውስጥ መሸገች።
ትንሽ ቀማምሳ እቤት ትመጣና
"ዕድሌ" ትለኛለች
ወይ አታቲዬ
"በጣም ጎበዝ፣ በጣም ተንከባካቢ፣ በጣም ጀግና እና ታታሪ እንዳታገቢ እሺ... ድንገት ካጣሺው ትዝታው እና እጦቱ አያራምድሽም"
እሺ አታቲዬ
"ዕድሌ... "
አቤት አታቲዬ
"ስታገቢ ተራ፣ ከሰው የተለየ ጉብዝና ያላየው፣ የትም የሚገኝ፣ የትም ያለ፣ ከብዙ ሰው የማይለይ፣ መርሕ እና ግብ ያልታጨቀበት አግቢ እሺ፣ ብታጪው እንኳን ማንነትሽ አይናድም... እሺ ዕድሌ"
እሺ... እሺ... አታቲዬ
"