#አሌክስ_አብርሃም
#አልተዘዋወረችም
#New
"
አንዳንዴ፣ ያለፍኩበትን ከንቱነት ገና ሊጀምሩት የሚራኮቱ ጀማሪ ጅሎችን ስመለከት የሆነ የግሌ ሬዲዮ ጣቢያ መክፈትና ከጧቱ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ በጎርናና ድምፅ "ይህ የጅሎች ድምፅ ነው! እንደምን አደራችሁ ጅሎች?" ማለት ያምረኛል። ሁሉም ከእኔ ወዲያ ብልጥ ላሳር የሚባልባት አገር ዜጋ ነኝና ማንም መልስ አይሰጥም፤ ይኼንን ዝምታ ከብልጠት ይቆጥሩታል። እኔም "ዝምተኛ ነኝ" ስልና "ዝምተኛ ነው" ስባል ነበር የኖርኩት። ጅልነት የተደላደለ መኖሪያው የዝምታ ባህር ውስጥ መሆኑ የገባኝ ቆይቶ ነው "ጅል ዝም ቢል ብልህ ይመስላል!" ይባል የለ። በጊዜ ፈውስ እንዳናገኝ ቂል ነፍሳችንን በዝምታ ብልህ ስናስመስል መኖርን በተረት፣ በአሽሙር እና በዘፈን አስተማሩን (ተማማርን ማለት ይሻላል!) ዝምታና ማድበስበሱ ብልህ ያስመሰለው የጅል አገር ዜጋ ነኝ።
"
በአሌክስ አብርሃም
#Books
GET US
Assistant