ከሲኤምሲ ወደ አያት አደባባይ በሚወስደው ሀይዌይ ዳር የሚገኝ፣ ከአጠገቡ መሪ ገበያ አለ። በጎን በኩል ወደ 72፣ ጎሮ፣ ሰሚት፣ ፍየል ቤትና ፊጋ የሚወስድ ሰፊ አስፋልት አለ። ከጀርባ ቤተ ክርስቲያንና መስጅድ አምስት ደቂቃ ቢፈጅ ነው። ከፊት ለፊት አስፋልት ተሻግሮ ጥምቀተ ባሕሩ ላይ በአሁኑ ሰአት ውብ መናፈሻ እየተገነባ ይገኛል። ሊፍቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ። ምን ቀረ? አሃ፣ ፎቶው ላይ ያለውን ስፖርት ሜዳ አዩት? በኮምፓውንዳችን ውስጥ ነው። ወረዳው፣ ክ/ከተማው እና መብራት ሀይል በእግር ቢበዛ 15 ደቂቃ ቢፈጅ ነው። ውሀና ፍሳሽ፣ ሰነዶች፣ ሱፐር ማርኬቶች፣ ዳቦ ቤቶች በጣም ቅርብ ናቸው። ባንኮችና ኤቲኤም እዚሁ ግራውንድ ላይ ያገኟቸዋል። የከበርቻቻና የቁርጥ ቤቶች ከፈለጉ ወደ ሲኤምሲ ወይም ወደ አያት አደባባይ መሄድ አለቦት። ሀያና ሠላሳ ደቂቃ ዎክ አርገው ያገኟቸዋል። ለስላሳና ቢራ የመሳሰሉትን ግራውንድ ላይ ከሚገኘው ግሮሰሪ ያገኛሉ። የመጨረሻው 13ኛ ፎቅ ላይ ነን። ከላይ ፍሳሽ የሚያፈስቦት ወይም የሚጨፍርቦት ወይም ቡና የሚወቅጥቦት የለም። አሃ፣ የረሳሁት ታዋቂውና ተሸላሚው ያኔት ሆስፒታል በመኪና ሁለት ደቂቃ ብቻ ይፈጃል። አያት አደባባዩ ላይ ነው። እናሳ ዋጋችን አይበዛም አይደል? ይደውሉ፣ በጨዋነት አስተናግዶታለሁ።