ከሲኤምሲ ወደ አያት አደባባይ በሚወስደው ሀይዌይ ዳር የሚገኝ፣ ከአጠገቡ መሪ ገበያ አለ። በጎን በኩል ወደ 72፣ ጎሮ፣ ሰሚት፣ ፍየል ቤትና ፊጋ የሚወስድ ሰፊ አስፋልት አለ። ቤተ ክርስቲያንና መስጅድ የአምስት ደቂቃ የእግር መንገድ። ከፊት ለፊት አስፋልት ተሻግሮ ጥምቀተ ባሕሩ ላይ በአሁኑ ሰአት ውብ መናፈሻ ተገንብቷል። ሊፍቶች ሥራ ጀምረዋል። ፎቶው ላይ ያለው ስፖርት ሜዳ በኮምፓውንዳችን ውስጥ ነው። ወረዳው፣ ክ/ከተማው እና መብራት ሀይል በእግር 15 ደቂቃ ቢፈጅ ነው። ውሀና ፍሳሽ፣ ሰነዶች፣ ሱፐር ማርኬቶች፣ ዳቦ ቤቶች በጣም ቅርብ ናቸው። ባንኮችና ኤቲኤም እዚሁ ግራውንድ ላይ ያገኟቸዋል። የከበርቻቻና የቁርጥ ቤቶች ከፈለጉ ወደ ሲኤምሲ ወይም ወደ አያት አደባባይ መሄድ አለቦት። ሀያና ሠላሳ ደቂቃ ዎክ አርገው ያገኟቸዋል። ለስላሳና ቢራ የመሳሰሉትን ግራውንድ ላይ ከሚገኘው ግሮሰሪ ያገኛሉ። የመጨረሻው 13ኛ ፎቅ ላይ ነን። ከላይ ፍሳሽ የሚያፈስቦት ወይም የሚጨፍርቦት ወይም ቡና የሚወቅጥቦት የለም። ያኔት ሆስፒታል በመኪና ሁለት ደቂቃ ብቻ ይፈጃል። አያት አደባባዩ ላይ ነው። ዋጋችን አይበዛም። ይደውሉ፣ ባለቤት ነኝ።