መጽሐፉ የተጻፈበት መነሻ ምክንያት
በዚህ በቴክኖሎጂ በረቀቀና በብርሃን ፍጥነት በሚለዋወጥ ዓለም ውስጥ ትውልዱ ወጣቱ ትልቅ ጫጫታና ውዥንብር ውስጥ ይገኛል ። የባዶነት፣ የብቸኝነት እና “ወደ ኋላ ቀረሁ” የሚል የጭንቀት ስሜት ውስጥ እየወደቀ ያለውን እና
ከትዝታ እስር ቤት መውጣት ለማይችሉ እና በትናንት ስብራት ውስጥ ለታሰሩ ወጣቶች እውነተኛ የመውጫ መንገድ ለማሳየት ነው።
የመጽሐፉ ዋና መልዕክት
ውድ ታዳሚዎቼ፣ እያንዳንዳችን ሕይወት በታላቁ ፈጣሪ እጅ ሊጻፍ የሚገባው ድንቅ መጽሐፍ ነው። ምናልባት የመጀመሪያዎቹ የሕይወታችን ምዕራፎች በሌሎች ሰዎች ስህተት፣ በትናንት ቁስል ወይም በወላጆች ስብራት ተጽፈው ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ያ ታሪክ ዛሬያችንን እንዳይበክልና ነገያችንን እንዳይቀማን የመከልከል ሙሉ ሥልጣን በፈጣሪ ጸጋ ተሰጥቶናል። ስለዚህ ወጣቱ የእኔ የሚለውን የሕይወት ምዕራፍ መኖር እንዲችል ለማገዝ የተፃፈ የስነ ልቦና መፀሀፍ ነው።