አፓርትመንቱ
የሚገኘው በቦሌ ወሎ ሰፈር አካባቢ G+20 ሆኖ በተገነባ፣ የከተማው እጅግ ውብ እይታ ባለው ዘመናዊ የመኖሪያ ህንፃ ላይ ነው። ህንፃው ለነዋሪዎች ዘመናዊ እንግዳ መቀበያ፣ የከርሰምድር ውሃ፣ 3 ሊፍት፣ 3 ቤዝመንት የመኪና ማቆሚያ፣ ጀነሬተር እና ዘመናዊ የህንፃ አስተዳደር አገልግሎቶችን ያካትታል።
ቤቱ በ15ኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ እጅግ ማራኪ የከተማ እይታ ያለው ፣ ነፋሻማ እና ብርሃናማ ነው። ህንፃው በያዝነው አመት ለነዋሪዎች ርክክብ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ይገኛል።