ቀጣሪ - ከገበሬው የንብ ሀብት ልማት ኃ/የ/የ/ማ
ከገበሬው የንብ ሀብት ልማት ኃ/የ/የ/ማ በንብ ሀብት ለማት እና የማርና ሰም ንግድ ላይ የተሰማራ ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ የማር ውጤቶችን ቀጥታ ከገበሬዎች በመግዛት ለተጠቃሚዎች ያቀርባል። በተጨማሪም ለገበሬ የሚያስፈልጉ የንብ ሀብት ልማት ግብዓቶችን ያቀርባል። በዚህም ከገበሬው እድገት ጋር በተሰላሰል ለማደግ ተግቶ የሚሰራ ድርጅት ነው።
ድርጅታችን አንድ ሰራተኛ ለአስተዳዳሪና ሽያጭ ሥራ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት የምታሟሉ ሙሉ መረጃችሁን (ሲቪ፣ የትምህርት ማስረጃ ከነ ግሬድ ሪፖርት፣ የስራ ልምድ፣ ሌሎች አስፈላጊ ተብሎ የሚታሰቡ መረጃዎች) በቴሌግራም ቁጥር ይላኩልን።